Theodros Atlaw7 reviews25 followersFollowFollowDecember 4, 2021እንደ ግሩም ግጥም፣ በተነበበ ቁጥር ሌሎች ትርጓሜዎችን የሚያነቃው፣ ሌሎች ትዝታዎችን የሚቀሰቅሰው፣ ሌሎች ስሜቶችን የሚያባንነው “ወሪሳ”፣ የዓለማየሁ ከቀድሞው/ከነባሩ ሥነ ጽሑፍ የተለየ ነገር የመስጠት ጠባይ ይበልጥ በርትቶ የታየበት ድርሰት ነው፡፡ በዚህ ድርሰት ዓለማየሁ እንደ ጋብሬል ጋርሺያ ማርቆስ፣ እንደነ ሁሊዮ ኮርታዛር፣ ምትሃታዊ እውነታዊ/Magic realist ሆኖ ይመጣል፤ እንደ ፋንታሲ ደራሲዎች ከእውናዊው ዓለም የተለየ የአሰፋፈር፣ የአኗኗር፣ የአስተዳደር ደንቦች ያሏቸውን ምናባዊ መቼቶችም ይሰጠናል፡፡የ“ወሪሳ” ታሪክ የሚከናወንባቸው መቼቶች፣ የዘራፊዎቹ ምድር ‘ወሪሳ’ እና የፀበኞቹ ምድር ‘እሪ በከንቱ’ በጠላትነት የሚተያዩ ተጎራባች መንደሮች ናቸው፡፡ የእነዚህ ዓለማት እውነታ ከምንኖርበት ዓለም እውነታ የተቀዳም ቢሆን፣ የአንድ ማኅበረሰብ መለያ ሆኖ ሲመጣ ግን ቢያንስ የኛ እውነታ ነው ብለን ከምናምነው ጋር ይማታብናል፡፡ ወሪሳዎች የሌብነትን፣ የነጣቂነትን፣ የዘራፊነትን ትክክለኛ ማኅበራዊ እሴትነት እያጸደቁ፣ እሪ በከንቱዎች ደግሞ ወንድ ልጅ ካልተጣላ፣ ካልገደለ፣ ካልተካሰሰ ... ምኑን ወንድ ሆነው የሚል ማኅበራዊ እሴት እያወደሱ የሚኖሩ ናቸው፡፡በእኔ ንባብ “ወሪሳ” ተቀጣጣቢ (Parodist) ድርሰት ነው፤ ታሪካችንን፣ ፖለቲካችንን፣ ማኅበራዊ ግንኙነታችንን፣ ትምህርታችንን በተውላጠ ታሪኮች (Alternate History) እንደአዲስ እንድናየው፣ እየሳቅን እንድንሳቀቅበት፣ መጪውንም እንድንፈራው ያደርገናል፡፡ በ“ወሪሳ” የአለማየሁ ገላጋይ ቀልድ አዋቂነት፣ በቋንቋ እንዳሻው የመጫወት ብቃት፣ የተረት (የተውላጠ ታሪክም ጭምር) ፈጣሪነት አቅም የታየበት ድርሰት ነው፡፡
Leyu7 reviewsFollowFollowAugust 17, 2015መውጣት የማይቻልበት፣ ቀማኛነት የሰፈነበት ፣ እውነቱ-ውሸት ውሸቱ-እውነት የሆነበት "Dystopian" ዓለም/አካባቢ የተሳለበት ነው:: ከሁሉም በላይ የተለያዩ ያለፉ ታሪኮች በተለያዩ ስዎች ሲነገሩ ያላቸው ተምሳሌያውነትና ሊሰጣቸው የሚችለው የተለያየ ትርጉም ብዙ የሚሄድበት ነው::africa amharic dystopia ...more