Jump to ratings and reviews
Rate this book

ከሰማይ የወረደ ፍርፍር

Rate this book
ድንቅ የፋንታሲ (“ፈንጠዚያ”) ሥራዎች የተካተቱበት ስራ ነው::

247 pages, Paperback

First published December 1, 2009

6 people are currently reading
108 people want to read

About the author

አዳም ረታ

13 books186 followers
አዳም ረታ በ1950 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ተወለደ። በትምህርት አለም - በጂኦግራፊ የመጀመሪያ ዲግሪውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተቀብሏል። ሁለተኛ (የማስተርስ) ዲግሪውን ደግሞ በውጭ ሀገር አግኝቷል። የሚፅፈው በአብዛኛው አጫጭር ልቦለዶችን ቢሆንም ግጥሞችንም ይፅፋል። በተለያዩ ጊዜያት ግጥሞቹ በተለያዩ መፅሔቶች ላይ ታትመዋል። ያልታተሙ ግጥሞችም አሉት።

‹ማሕሌት›፣ ‹አለንጋና ምስር›፣ ‹እቴሜቴ ሎሚ ሽታ›፣ ‹ከሰማይ የወረደ ፍርፍር›፣ ‹ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ›፣ ‹ሕማማትና በገና› የተሰኙ የአጫጭር ልብወለዶች ስብስብ መጽሀፍትን በግሉ አሳትሟል፡፡

የአዳም የረዥም ልብወለድ ሥራ የሆኑት ‹ግራጫ ቃጭሎች› እና ‹መረቅ›ም በብዙ አንባቢዎች ዘንድ ተወዳጅ ናቸው፡፡

አዳም ረታ በአጻጻፍ ስልቱ ልዩ፣ በቋንቋ አጠቃቀሙ ማራኪ እና በሚያነሳቸው ሀሳቦች ምጡቅ ደራሲ እንደሆነ የስነ-ጽሑፍ ባለሙያዎችና የሥራዎቹ አንባቢዎች ይመሰክራሉ፡

Ratings & Reviews

What do you think?
Rate this book

Friends & Following

Create a free account to discover what your friends think of this book!

Community Reviews

5 stars
18 (39%)
4 stars
21 (45%)
3 stars
5 (10%)
2 stars
1 (2%)
1 star
1 (2%)
Displaying 1 of 1 review
Profile Image for ntnl.
122 reviews19 followers
November 6, 2020
ከሰማይ የወረደ ፍርፍር እጅግ ድንቅ እና ጥልቅ ፅሑፍ ነው። የጊዜ እንቆቅልሽ.. የተሰጠንና እኛ የምንፈልገው.. ህልም እና እውነት.. ታች እና ላዩ.. ሁሉ ተደባልቆ ሕይወት.. እስትፋስ ሲዘራበት..

አዳምን የሚያነብ ሁሉ.. ቀጥሎ ምን ይሆናል የሚል ጥያቄ አያሳስበውም.. ነገር ግን በእያንዳንዱ ገፅ ውስጥ.. በያንዳንዱ መስመር.. በያንዳንዱ ቃላትና ዝርዝር ውስጥ ይኖራል.. ይተነፍሳል.. ሕይወትን ያጣጥማል.. (የሚጣጣም ነገር ሲገኝ.. መራራው መራራ፣ ሻካራው መሻከሩ አይቀርልህም).. ከሰማይ እንደ ወረደው ፍርፍር።

ድንኳኑን ማን እንደሰፋውም እንዳይረሳ.. አደራ። የዛፉ ምቀኝነት.. የልጅቷ ልብ አልባነት.. ሌሎችም ሌሎችም...
This entire review has been hidden because of spoilers.
Displaying 1 of 1 review

Can't find what you're looking for?

Get help and learn more about the design.