Jared Donis333 reviews58 followersFollowFollowDecember 28, 2021‘ከዕለታት ግማሽ ቀን’ የሚለውን ስራውን ከጨርስኩ በኋላ ነው ለመጀመርያ ግዜ ዶክተር አሸብርን ፈልጌ ያነበብኩት። አሌክስ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ሕይወታችንን አጉልቶ በማሳየት እንደማይታማ ተደጋግሞ የተረጋገጠ ጉዳይ ነው። ‘ዶክተር አሸብር’ ውስጥ ያሉት ታሪኮችም በዚህ ክህሎቱ አሌክስን በሰፊው ያስተዋወቁን የበኩር ስብስቦቹ ናቸው። አብዛኞቹን ፌስቡክ ላይ እንዳስነበበን አስታውሳለሁ፤ በደጉ ዘመን። ያው እንግዲህ አብዛኞቹ በስብከት የታጨቁ፣ ጥቂቶቹ ደግሞ ከፌስቡክ በዘለለ ለሕትመት መብቃት የሌለባቸው ስራዎች ቢኖሩበትም የአብዛኞቹን አጨራረስ በማራኪ መንገድ ስላቀረበው የማንበብ ፍላጎቴን አልቀነሰውም። በተረፈ ‘ዶክተር አሸብር’ን አንብቦ ‘ከዕለታት ግማሽ ቀን’ን ያነበበ ሰው አሌክስ ምን ያህል ራሱን እንዳሻሻለ ይገነዘባል። እኔም ወደ ኋላ ተመልሼ የመጀመሪያ ስራውን ያነበብኩት ያንን ለማረጋገጥ ነው። ለውጥማ አለ! መልካሙን ሁሉ ለአሌክስ እመኛለሁ። አብርሃም ከሚለው ገጸ ባህሪው ወጥቶ ሌሎች ወጥ ስራዎችን እንደሚያበረክትልንም ተስፋ አደርጋለሁ።
Estifanose Sahilu10 reviewsFollowFollowApril 17, 2026Read this when i was in 6th grade and re-read it several times later. Banger of a book every time!amharic favorites