Home
My Books
Browse ▾
Recommendations
Choice Awards
Genres
Giveaways
New Releases
Lists
Explore
News & Interviews
Loading...
Community ▾
Groups
Quotes
Ask the Author
People
Sign in
Join
Jump to ratings and reviews
Want to Read
Buy on Amazon
Rate this book
ዐፄ ምኒልክና የኢትዮጵያ አንድነት
ተክለጻድቅ መኩሪያ
4.00
26 ratings
1 review
Want to Read
Buy on Amazon
Rate this book
ስለታላቁ ንጉስ አፄ ምኒልክ ለኢትዮጵያ አንድነት ክብርና ብልፅግና ስልጣኔ እምነት ያደረጉትን ታቅ ክንውኖችና አስተዋፅዎችን የከተበ ትልቅ የታሪክ መጸሐፍ።
Paperback
Book details & editions
21 people are currently reading
607 people want to read
About the author
ተክለጻድቅ መኩሪያ
4 books
19 followers
Follow
Follow
ተክለጻድቅ መኩርያ በ 1906 ዓ.ም. በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ አሳግርት ልዩ ስሙ ሳር አምባ በተባለ ሥፍራ ተወለዱ።
ዕድሜያቸው ለትምሕርት ሲደርስ መጀመሪያ ከአባታቸውና ቀጥሎም በአጥቢያቸው ባህላዊውን ትምሕርት እስከቅኔ ያለውን ቀስመዋል። ከዚያም አዲስ አበባ መጥተው አሊያንስ ፍራንሴዝና ተፈሪ መኮንን ትምሕርት ቤት ገብተው የጊዜውን የትምሕርት ደረጃ አጠናቀዋል።
ኢጣልያ አገራችንን የወረረች ጊዜም በየካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም. ፍጅት ተይዘው ወደ ሶማሌ ደናኔ ተግዘው ለሦስት ዓመታት ታስረዋል። ከነጻነትም መልስ አገራቸውን በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች አገልግለዋል።
መጀመሪያ ተቀጥረው ያገለገሉት በትምሕርትና ሥነጥበብ ሚኒስቴር ነበር። እዚያም ሳሉ በአገራችን ሰው የተጻፈ የአገራችን ታሪክ አንድም ባለመኖሩ በቁጭትና በመቆርቆር ነበር ‘መጻፍ አለብኝ’ ብለው በደንብ ከሚታወቀው ከቅርቡ ጊዜ በቅጡ ወደማይታወቀው የሩቁ ዘመን መጻፍ የጀመሩት። የመጀመሪያውን መጽሐፍ “የኢትዮጵያ ታሪክ ከዓፄ ቴዎድሮስ እስከ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ” የሚለውን በ 1938 ዓ.ም. አሳተሙ። ከጫፍ እስከ ጫፍ ጽፈው የመጨረቻውን መጽሐፍ፣ የታሪካችን መጀመሪያ የሚሆነውን “የኢትዮጵያ ታሪክ ኑብያ-አክሱም-ዛጉዬ እስከ ዓፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት” የሚለውን በ1951 ዓ.ም. አቅርበዋል። እኒህኑ መጻሕፍት ትምሕርት ሚኒስቴር ታሪክ ለማስተማሪያ በትምሕርት ቤት ተጠቅሞባቸዋል።
ተክለጻድቅ ከታሪክ ውጭ የጻፏቸው “የሰው ጠባይና አብሮ የመኖር ዘዴ” እና በሚዮቶሎዢያ (mythology) ላይ ያተኮረ “ከጣዖት አምልኮ እስከ ክርስትና” የሚሉም መጽሐፎች አሏቸው።
ተክለጻድቅ በምድር ባቡር በዋና ጸሐፊነት፥ በቤተ መጻሕፍት ወመዘክር ዋና ሥራ አስኪያጅነት፥ እንዲሁም በፈረንሳይ፥ በእስራኤል፥ በዩጎዝላቪያ በዲፕሎማሲ ሥራ በመጨረሻም የትምሕርትና የባህል ሚኒስቴር ሆነው አግልግለዋል። በፈቃዳቸው ጡረታም ከወጡ በኋላ በምርምር የታገዙ ሦስት ታላላቅ የታሪክ ሥራዎችን አቅርበዋል።
ተክለጻድቅ ከረጅም የአገልግሎት ዘመን በኋላ በተወለዱ በ ሰማንያ ስድስት ዓመታቸው ሐምሌ 16 ቀን 1992 ዓ.ም. አርፈዋል።
የተክለጻድቅን ሥራዎች ዋጋ የምንሰጣቸው ለሚከተሉት ምክንያቶች ነው፦
• ታሪክን ከተተበተበበት ልማዳዊ አጻጻፍ ነጻ አውጥተው በሰገላዊ መንገድ መጻፍ በመጀመራቸው
• አገራዊውን መረጃም ሳይተው በውጭ ቋንቋ በጣልያንኛ፥ በፈረንሳይኛ፥ በእንግሊዝኛ ጭምር ያለውን ሁሉ ተጠቅመው ከስር እስከጫፍ የአገሪቱን ታሪክ በመጻፋቸው
• እኒህን ሁሉ መጻሕፍት የጻፉት በመደበኛ የቀለም ትምሕርት ቤት ሳይሰለጥኑ፥ በከፍተኛ የመንግሥት ሥራና ኀላፊነት ተጠምደው፥ ያላቸውን የምዝናኛ ጊዜ ሁሉ ሰውተው ቁም ነገር በመሥራታቸው
• በተለይም ከአሥራ አምሥት ዓመታት በላይ የደከሙበት “የግራኝ አሕመድ ወረራ” የተሰኘው መጽሐፋቸው በመቶ አምሳ አምሥት ምዕራፎችና ስምንት መቶ አርባ ገጾች በጽሑፍ፥ በካርታ፥ በሠንጠረዥ፥ በፎቶግራፍ መረጃዎች ተሞልቶ ሥርዓት ባለው መልክ ታሪኩ ትንትን ተደርጎ የተሠራ ግዙፍ ሥራ በመሆኑ
Ratings
&
Reviews
What do
you
think?
Rate this book
Write a Review
Friends
&
Following
Create a free account
to discover what your friends think of this book!
Community Reviews
4.00
26 ratings
1 review
5 stars
12 (46%)
4 stars
8 (30%)
3 stars
1 (3%)
2 stars
4 (15%)
1 star
1 (3%)
Search review text
Filters
Displaying 1 of 1 review
Sintayehu Lijalem
1 review
Follow
Follow
Currently reading
January 24, 2023
በጣም ደስተኛ ነኝ፡፡
Displaying 1 of 1 review
Join the discussion
Add
a quote
Start
a discussion
6
questions
Can't find what you're looking for?
Get help and learn more about the design.
Help center