Jump to ratings and reviews
Rate this book

መንግሥትና የሕዝብ አስተዳደር

Rate this book
ይህ መጽሐፍ ከመስራት የተነሳ የሰው ልጅ እንዴት ከተፈጥሮ ጥገኝነት ተላቅቆ ከኋላ ቀር አኗኗር ወደ ተሻለ ሕይወት እንደሚለወጥ የሚያስረዳ ሲሆን የዓለም ሕዝቦች የዕውቀታቸውና የሀብታቸው ደረጃ ከፍና ዝቅ ያለ መሆኑ ምክንያቱ ከጦርነት የተነሳ ነው ይላል። ጦርነቱንም የሚነሱ ነገሥታትና አለቆቹ ሁሉ ልባቸው ሀብት እንደፈለጉ አይገልፅም። ነገር ግን ስም ለመፈለግና ለማግኘት ወይም ሀይማኖቱን ለማስፋፋት ወይም የተጠቃውን ለመርዳት አስመስለው ይነሳሉ።

የጦርነት ሁሉ ፍፃሜ ምኞት ግን መዝረፍና ማስገበር ነው። ይህንንም ሲሉ ዕውቀታቸው የሰፋ ነገሥታትም ቢሆኑ መዝረፍን አይተዉም። አዘራረፋቸው ግን የዕውቀት አዘራረፍ ነው እያለ በሰፊው ያወሳል።

Paperback

First published January 1, 1923

7 people are currently reading
146 people want to read

About the author

ነጋድራስ ገብረሕይወት ባይከዳኝ በ1879 ዓ.ም. በአድዋ አካባቢ ተወለዱ፡፡ ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ ኤርትራ ውስጥ በሚገኘው የሲዊድን ሚሽን ከተማሩ በኋላ ወደ ጀርመንና አውስትራሊያ በመሄድ የሕክምና ትምህርታቸውን አጠናቀቁ፡፡ ከጀርመን ሚሽን ጋር ወደ ኢትዮጵያ በመመለስ በዓፄ ምኒልክ ቤተመንግሥት ፀሐፊ በመሆን ሠርተዋል። የምኒልክ ሐኪም ለነበረው ጀርመናዊ ዶክተር አስተርጓሚ ሆነው ሲያገለግሉ ከእቴጌ ጣይቱ ጋር በነበራቸው አለመግባባት አገር ለቀው ወደ ሱዳን ተሠደዱ፡፡ ከዛም ለሱዳን መንግሥት የሀገር ውስጥ ደኀንነት ሲሠሩ ቆይተው ወደሀገራቸው በመመለስ በቤተመንግሥት ውስጥ ማገልገል ጀመሩ፡፡ በመቀጠልም የድሬዳዋ ጉምሩክ ኃላፊ ሆነው ተመድበው በራስ ተፈሪና በሌሎች ተቀናቃኞች ወገኖች ተፈጥሮ በነበረው ግጭት ራስ ተፈሪን ወግነሀል በሚል ከኃላነታቸው ተነሱ፡፡

እኝህ የኢኮኖሚ ፈላስፋና የሕክምና ምሁር በ1912 ዓ.ም. በኀዳር በሽታ ሕይወታቸው ቢያልፍም “መንግሥትና የሕዝብ አስተዳደር” በሚለው ዝነኛ መጽሐፋቸው የሀገሪቱን የውስጥ ጉዳይ አስተዳደርና ኢኮኖሚ እንዲሁም በትምህርት ላይ ፍጹም ለውጥ እንዲኖር አሳስበዋል፡፡ መጽሐፋቸው ለመጀመሪያ ጊዜ የታተመው በአቶ ጳውሎስ ኞኞ አማካይነት ነው፡፡

Ratings & Reviews

What do you think?
Rate this book

Friends & Following

Create a free account to discover what your friends think of this book!

Community Reviews

5 stars
6 (50%)
4 stars
3 (25%)
3 stars
3 (25%)
2 stars
0 (0%)
1 star
0 (0%)
Displaying 1 - 2 of 2 reviews
Profile Image for ntnl.
122 reviews19 followers
June 24, 2020
ገብረሕይወት ንጉሱና ሕዝቡን (ሀገሩን) የመምከር ድፍረቱ እና አቅሙ እንደነበረው ይሄ መጽሐፍ ማስረጃ ነው። በሚያነሳው ሀሳብ ውስጥ ከባህል፣ ከሀይማኖት እና ከልማድ ስርዓት ነጻ ሆኖ ለመጻፍ የሚያረገው ጥረት በግልጽ ይንጸባረቃል። 'መች ተወለደ ሳይሆን መች አወቀ' ይሉሃል ይሄ ነው።
This entire review has been hidden because of spoilers.
Displaying 1 - 2 of 2 reviews

Can't find what you're looking for?

Get help and learn more about the design.