Jump to ratings and reviews
Rate this book

ኅሠሣ

Rate this book
"ይህ “ኀሠሣ” የተሰኘው የሕይወት ተፈራ መጽሐፍ፥ በውብ ሥናዊ የብዕር አተራረክ፥ የኢትዮጵያን “የባሕል”፥ “የትምህርት”፥ “የፍልስፍና”፥ እንዲሁም“ የሃገረ-ሰብእ” ወዘተ. ይትበሃሎችን መሠረት አድርጎ የተነሳ ሥነ-ጽሑፋዊ ሥራ ነው። ለትረካዋ ዋና ማዕከል ባደረገችው በጥንታዊው የአብነት ትምህርት ሥርዓት ውስጥ ቤተክርስቲያን ከጥንትም የትምህርት ማዕከል መሆኗን፥ ለመንፈሳዊም ሆነ ለምድራዊ አገልግሎት የሚሆኑ ችሎታ ያላቸውን ልጆች መርጣ፥አሳድጋ እና አስተምራ ሠናይ የሆኑ ሊቃውንትን ስታፈራ መቆየቷን በዋና ገፀ-ባሕርዩ የሕይወት ተሞክሮ ተመርኩዛ ታሳየናለች።
መጽሐፉ በሥነ-ጽሑፋዊ ለዛው የሚደነቀውን ያህል፥በጽሑፍ መንፈሱ፥ የኢትዮጵያን ጥንታዊ ትምህርት ከአውሮፓው የትምህርት ፍልስፍና ጋር በማወዳደር፥ በማነጻጸር ወይም በማፎካከር ዘይቤ የቀረበ ሳይሆን፥ የተዋሥዖ ሥነ-ዘዴን ተከትሎ ሥርዓተ ወጉን እንዳለ በመተረክ በሚያስደምም መልኩ የተጻፈ ሥነ-ጽሑፋዊ ሥራ ነው። ይህንን ለማድረግም፥ ደራሲዋ ወደታላላቆቹ ጥንታውያን የቅኔ የምስክር መካናት በአካል በመሄድ የጥናት ሥራዋን አካሂዳለች፥ ጠይቃለች፥ ተወያይታለች፥ ተደንቃለች። በየሊቃውንት መንበረ ጉባኤዎቹ ውስጥ ያገኘችውን፥ ያስተዋለችውን እና የተደነቀችበትን ታላቅ ቁም ነገር፥ እንዲሁ በደረቅ የጥናት ወረቀት መልክ ከማቅረብ ይልቅ፥ ልበ-ወለዳዊ አጻጻፍን እና የልበ-ወለድ አላባውያንን በመጠቀም መጻፍን መርጣለች። ይህም ለመጽሐፉ ሳይሰለች የመነበብ ጸጋ ይጨምርለታል። የመጽሐፉ ትልቅ ረድኤት፥ የኢትዮጵያን የፍልስፍና መሠረት “ቅኔን”፥ ከነሥርዓቱ በመጠኑም ቢሆን ማስተዋወቁ ላይ ነው። እንደ እውነቱም፥ የኢትዮጵያ ፍልስፍና ቢመረመር፤ የአቀራረብ መንፈሱ በሊቃውንቱ ቅኔ እና በቅኔ ወንበር ላይ እንደሚገኝ፥ የሕይወት ተፈራ መጽሐፍ ሁነኛ ምስክር ሆኖ ያስረዳናል። ቅኔ የብዙ ጻማ (ልፋት) ውጤት ነው። ቅኔ፤ የአእምሮን ጥንካሬና፥ ብስለት፥ የምናብን ርቀት፥ ማስተዋልን፥ መተንተንን፥ መግለጽን፥ መጠየቅን እና መራቀቅን አካቶ የያዘ የአእምሮ ጎዳና ሲሆን፥ ከተፈጥሮ ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ጥበብም ነው። የምዕራቡ ዓለም የፍልስፍና ታሪክ ዘጋቢዎች “ፍጥረት የፍልስፍና ግኝት ናት” እንደሚሉት፥ እኛም “ፍጥረት የቅኔ ግኝት ናት፤” ማለት እንደምንችል፥ ይህ የሕይወት ተፈራ መጽሐፍ ትልቅ ዋቢ ሆኖ ያስረዳናል።"
ዶከተር ዳኛችው አሰፋ

"ኢትዮጵያ በረጅም ታሪኳ ካፈራቻቸው ትውፊቶቿ አንዱ የቤተ ክህነት ትምህርት ነው። የኢትዮጵያ ታሪክና ሥልጣኔ በተጻፈ ቁጥር የሚዘከሩት፤ የቁሳዊው ሥልጣኔ ነፀብራቅ የሆኑት ቅርሶች ናቸው። ነገር ግን የቤተክህነቱ ትምህርት በዘመናት ጉዞው የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን፤ ቅዱስ ያሬድና ተዋነይን፤ መምህር ኤስድሮስን፤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫን፤ መምህር አካለወልድን እና ሌሎችንም ብርቅየ ቅርሶችና የበቁና የረቀቁ ሊቃውንት ያፈራ ነው።
ሕይወት በዚህ ‘ኅሠሣ’ በተሰኘ መጽሐፏ የምታሳየን እኒህ ቅርሶችና ሊቃውንት ዘወትር ሊሚወሱበት ታሪክ እንዲሁም ለሚደነቁበት ልህቀት የበቁት የልጅነት ሕልማቸውን የሕይወታቸው ግብ አድርገው ትምህርቱ የሚጠይቀውን መከራ ችለው ፈተናውን ተወጥተው ሕልማቸውን የሚያሰናክል ፍላጎትን ገትተው በታላላቆቻቸውና በመምህሮቻቸው ተገስጸውና ታንፀው መሆኑን ነው። ሕይወት ይህን ታሪካዊ እውነት በልብ ወለድ መልክ ስታቀርበውም ሁነኛ መቼት መርጣ ነው። ከ20ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በባለቤቱ ሳይቀር የተረሳውን ይህን የታሪካችን ዓይነተኛ ትውፊት የዘመናችን ትውልድ በሚረዳው አተራረክ አቅርባዋለች።
የመጽሐፉ ውጤት ምን እንደሚሆን መተንበይ ከባድ ቢሆንም ሕይወት ግን ለዚህ ታሪካዊ የትምህርት ትውፊት ማንሰራሪያ የሚሆን የሕይወት እስትንፋስ ሰጥታዋለች።"
አበባው አያሌው (ረዳት ፕሮፌሰር)
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ

182 pages, Paperback

First published November 1, 2016

1 person is currently reading
110 people want to read

About the author

Hiwot Teffera

4 books95 followers
Born and raised in Harar, Ethiopia. Hiwot Teffera is author of two books that are now translated in to Amharic language.

Ratings & Reviews

What do you think?
Rate this book

Friends & Following

Create a free account to discover what your friends think of this book!

Community Reviews

5 stars
2 (25%)
4 stars
4 (50%)
3 stars
2 (25%)
2 stars
0 (0%)
1 star
0 (0%)
Displaying 1 - 2 of 2 reviews
1 review2 followers
Read
November 7, 2019
Reading it for the sake of my daughter ,Tough Amharic terms has been used.
This entire review has been hidden because of spoilers.
Profile Image for Martha H. Kidane.
46 reviews30 followers
July 21, 2017
It is a captivating story written about Qine and Ethiopia's traditional school system. It is written in compelling manner hence the translation a compelling one. However, what really sets this version apart from the English is that the caution the translator took in translating the English version to make sense as to the Ethiopia 100 years back, which rewinds the leap the Amharic language took by exactly that many years. The translator has used different cautions in trying to do justice to Hiwot Teffera's book and I believe she has succeeded on that regard. Some narrations in the book might seem or sound lame for a person that has gone through the traditional system, but for the new reader such as myself not only is it informational and notable work for a person that wishes to know more about Ethiopia's traditional school system, the story and the way the characters are drawn, the stand they have in life and the wisdom they impart makes this book a wonderful read.
I hope the next reader enjoys too!
Displaying 1 - 2 of 2 reviews

Can't find what you're looking for?

Get help and learn more about the design.