Home
My Books
Browse ▾
Recommendations
Choice Awards
Genres
Giveaways
New Releases
Lists
Explore
News & Interviews
Loading...
Community ▾
Groups
Quotes
Ask the Author
People
Sign in
Join
Jump to ratings and reviews
Want to Read
Buy on Amazon
Rate this book
የዕውቀት ብልጭታ
ከበደ ሚካኤል
4.00
7 ratings
0 reviews
Want to Read
Buy on Amazon
Rate this book
Unknown Binding
Published January 1, 1950
Book details & editions
Loading...
Loading...
About the author
ከበደ ሚካኤል
2 books
12 followers
Follow
Follow
ከበደ ሚካኤል ጥቅምት 23 ቀን 1909 ዓ.ም በሰሜን ሸዋ -- ደብረ ብርሃን ከተማ አካባቢ ገርም ገብርኤል አጥቢያ ተወለዱ።
በህፃንነታቸው የመጽሐፍ ቅዱስን ልዩ ልዩ ታሪኮች በወግ መልክ በመተረክ እንደ አነፅዋቸው የመሰከሩላቸው እናታቸው ወ/ሮ አፀደ ሚካኤል ጀንዲ እስከ ዘጠነኛ አመታቸው ድረስ በባህላዊን የግዕዝ ትምህርት እንዲቀስሙ እንዳስቻሏቸው ይነገራል። ከበደ በ1918 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ መጥተው በእናታቸው ወንድም በአቶ ሰይፉ ሚካኤል ልዩ ድጋፍ በ"አሊያንስ ፍራንሴስ" በፈረንሣይኛ የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን፥ በላዛሪስ ሚሲዮንም የመለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል።
ከበደ ሚካኤል እስከ ጣሊያን ወረራ ዋዜማ ድረስ በነበረው የተማሪነት እና የወጣትነት ቆይታቸው ከመደበኛ ትምህርታቸው ባሻገር በትርፍ ጊዜያቸው ልዩ ልዩ የፈረንሳይኛ መጸሐፍትን በማንበብ የቋንቋ የንግግር ችሎታቸውን አዳብረዋል። አንድም - በዘመናቸው ከነበሩት ቀደምት ታዋቂ ኢትዮዽያውያን ምሁራን - የአለቃ አፅመ ጊዮርጊስን፥ የአለቃ ኪዳነወልድ ክፍሌን፥ የፕሮፌሰር አፈወርቅ ገ/ኢየሱስን፥ የነጋድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝን እና የነቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴን አዳዲስ ሓሳቦች ቀስመዋል። ከትምህርት ቤት መምህራኖቻቸው ይሰጡዋቸው በነበረ ልዩ ድጋፎችም የግሪክን የሮማውያንን፥ የእንግሊዝን፥ የፈረንሳይን፥ የጀርመንን፥ የሩሲያን እና የኢታሊያን ፈላስፎች ጠቢባንና ሳይንቲስቶች "ታላላቅ ሰዎች" መጻህፍት አንብበዋል መርምረዋል።
ከኢጣሊያ ወረራ 1929 -1933 ዓ.ም በኋላ በ"ነፃነት መዝሙር" -የቅኔ መንገድ ልዩ ተሰጥኦዋቸውን አሀዱ ያሉት ከበደ ሚካኤል ከሃገራችን ደራሲያን በላቀ መልኩ በዘመናዊ እሳቤና ሥነ ጽሑፋዊ ተሳትፎአቸው ከ16 በላይ የሚቆጠሩ ልዩ ልዩ የእውቀት ዘርፎች ፍልስፍና፥ ሥነመለኮት፥ ሥነ ትምህርት፥ ሥነምግባር፥ ሳይንስ፥ ሥነ ጥበባት፥ ቅኔ፥ ተውኔት "ብርሀነ ህሊና" በብእሮቻቸው መግለጫነት በአማርኛ፥ በፈረንሳይኛ፥ በእንግሊዝኛ፥ እና በጣሊያንኛ ቋንቋዎች ከ90 በላይ በታተሙ ከ200 በላይ ባልታተሙ ወጥና ትርጉም ድርሰቶቻቸው የኢትዮዽያን ዘመናዊ ሥነ ጽሑፍ አድማስ አስፍተዋል።
በአዳዲስ ሀሳቦች "አብራሄ ህሊና"ነት ሀዲስ ትውልድ ያፈሩት ፈላስማውና ባለቅኔው ከበደ ሚካኤል፥ ዘመናዊ ኢትዮዽያን ለማደራጀት በተደረገው ተጋድሎም በልዩ ልዩ የሚኒስትርነት ማእረጎች በግምባር ቀደምነት አገልግለዋል።
ፈላስፋ፥ ባለቅኔ፥ ፀሐፊ ተውኔት፥ ደራሲና አንጋፋው ጋዜጠኛ ከበደ ሚካኤል በአገራችን እንግዳና የመጀመሪያ የነበረውን የቀ.ኃ.ሥ. የ1957 ዓ.ም የሥነ ጽሑፍ ሽልማት በቀዳሚነት የተቀበሉ የ"ቀለም ሰው" ሲሆኑ፥ በዘላቂነት ሐዲስ ትውልድ ላፈራው የላቀ አስተዋፀኦዋቸውም የአ.አ.ዩኒቨርሲቲ ጥቅምት 26 ቀን 1990 ዓ.ም በሥነ ጽሑፍ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሸልሟቸዋል።
ክቡር ደ/ር ከበደ ሚካኤል ኅዳር 3 ቀን 1991 ዓ.ም በ82 ዓመታቸው አረፉ። "ሰኔ 21 ቀን የከበደ ሚካኤል መታሰቢያ ቀን" ሆኖ ተሰይሟል።
ምንጭ:ብርሀነመስቀል ደጀኔ 2000ዓ.ም ብራና.ማ.ቤ ካሌንደር።
Ratings
&
Reviews
What do
you
think?
Rate this book
Write a Review
Friends
&
Following
Create a free account
to discover what your friends think of this book!
Community Reviews
4.00
7 ratings
0 reviews
5 stars
4 (57%)
4 stars
1 (14%)
3 stars
1 (14%)
2 stars
0 (0%)
1 star
1 (14%)
Search review text
Filters
No one has reviewed this book yet.
Join the discussion
Add
a quote
Start
a discussion
Ask
a question